‘ሰንደቁ’ ላይ ያለው ‘አላማ’
የእነርሱ እና የእኛ ሕዳሴ
- የአክሱም ስልጣኔ
ከክርስቶስ ልደት በፊት 400 ዓመት አስቀድሞ የተጧጧፈው የአክሱም ስልጣኔ እስከ 10ኛው ክፍለ ዘመን ለመዝለቅ ችሎ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የአክሱም ስልጣኔ ስር መሠረት እና ውርሱ በቅጡ አይታወቅም፡፡ እስካሁንም ድረስ ቆመው ከሚገኙት እና አምልኮተ-መራባትን ያመለክታሉ ከሚባሉት ሀውልቶች በቀር ለትምህርትነት የሚበቃ፣ ወይም ከዚያ ዘመን ሲወርድ ሲወራረድ የመጣ ትውፊታዊ ቁምነገር አለ ለማለት የሚያስደፍር ግኝት የለም፣ - የዛግዌ ስልጣኔ
የአክሱም ስልጣኔ መውደቅን ተከትሎ የኢትዮጵያ የጨለማ ዘመን ለ200 ዓመታት ነገሠ፡፡ ከዚያም በመራ ተክለሃይማኖት አማካይነት የዛግዌ ስልጣኔ ተጀመረ፡፡ የዛግዌ ስልጣኔ ክርስትናን በማስፋፋት ላይ የተመሠረተ ሲሆን ትሩፋቱም የላሊበላ ውቅር ዐብያተ ክርስትያናት እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ትውፊታዊ ትምህርት ናቸው፡፡ የዛግዌ ዘመነ መንግስት ከአክሱም ስልጣኔ በተሻለ ሃይማኖት ቀመስ ቢሆኑም ጽሑፎች ተጽፈው ለቀጣዩ ትውልድ የተላለፉበት የመጀመሪያው ዘመን ነው ማለት ይቻላል፣ - ሰሎሞናዊ ስልጣኔ
ይሄንኛው የስልጣኔ ዘመን የአክሱም ዘመን ቀጣይ እና ሰሎሞናዊ ቤተሰብ ነን በሚሉ ነገሥታቶች የተመራ የስልጣኔ ዘመን ነው፡፡ የዚህ ዘመን መጨረሻ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት ነው፡፡ ይህ ዘመን ለቅርስነት ያስመዘገባቸው ነገሮች የሉም ማለት ይቻላል (የዘመነ መሳፍንት ቤተመንግሥታትም ቢሆኑ በዚህ ዘመን መሐል የተፈጠሩ የመከፋፈል ታሪኮች ናቸው፤) ሆኖም የአሁኒቷ ኢትዮጵያ የአሁኑን ቅርጿን የያዘችው በዚህ የስልጣኔ ዘመን ነው፡፡ በዚህ ዘመን አውሮጳውያን አፍሪካን ሲቀራመቱ ኢትዮጵያውያን ግን በእምቢተኝነት ራስ ገዝ አስተዳደር የፈጠሩበት ይህ ዘመን ነው፡፡ በዚህ ዘመን በተለይም ከአድዋ ድል በኋላ የተሠሩት ሥራዎች ኢትዮጵያን ከዘመናዊነት ጋር በማስተዋወቁ ረገድ መንገድ ጠራጊዎች ናቸው ማለት ይቻላል፤ በዚህ ዘመን ባቡር፣ ዘመናዊ ትምህርት፣ የጤና ብሎም የባንክ አገልግሎቶች እና ወዘተ ለመጀመሪያ ጊዜ በአገራችን ተዋውቀዋል፣ - የድኅረ ጣሊያን ኃይለሥላሴ ስልጣኔ
በዘመናዊት ኢትዮጵያ ውስጥ ጉልህ ስፍራ የሚኖራቸው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ አብዛኛውን ኢትዮጵያን የማዘመን ሥራ የሠሩት ከጣልያን የአምስት ዓመት ወረራ በኋላ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ሚያዝያ 27/1933 ንጉሡ ከስደት ሲመለሱ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት የ‘አዲስ ዘመን’ እንቅስቃሴያቸውን ጀመሩ፡፡ በወቅቱ ኢትዮጵያን ከሙሉ ፊውዳላዊ አስተዳደር በከፊል አላቀዋታል፣ በብሔር እና ሃይማኖት “መቻቻል” ላይ መጠነኛ ሚዛን እንዲሰጥ በሚል ሕገ መንግሥታቸውንም አሻሻለዋል፣ ፓርላማው ለሕዝቦች በመጠኑ የተከፈተውም በዚሁ ዘመን ነው፣ በተለይም ደግሞ ዘመናዊ ትምህርት ተስፋፋ፡፡ ከዚያም በላይ እስከአሁኑ የአባይ ግድብ፣ የቁጠባ ቤቶች (ኮንዶስ)፣ የአዲስ አበባ ቀለበት መንገድ እና ወዘተ መሠረታቸው የተጣለው በዚህ የስልጣኔ ዘመን ነበር፡፡ በተለይ በዚህ ዘመን የተፈጠረው የትምህርት እና የአንባቢነት ፋሽን በመግቢያችን ላይ የጠቀስናቸውን ዘመን አይሽሬ ጠበብት ለመፍጠር በቅቷል፣ - የማርክሲስት ስልጣኔ
የዚህ ዘመን ስልጣኔ ባለቤቶች የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመን ወጣቶች ሲሆኑ፣ ወደማርክሲዝም የመራቸውም በዘመኑ ለነበረው ፊውዳላዊ አስተዳደር የነበራቸው የመረረ ጥላቻ ነው፡፡ በዚህ ዘመን ለተመሳሳይ ርዕዮተ ዓለም (ማርክሲዝም/ማኅበረሰባዊነት) ነገር ግን በተለያየ ቡድን ተቧድነው ሲቆራቆዙ የነበረበት ዘመን ሲሆን፣ ለሁለት አሥርት ዓመታት በዘለቀው መቆራቆዛቸው ሳቢያ ‘ሰብኣዊ-ዘመናዊነት’ የጎደለው ዘመነ ስልጣኔ፣ ነገር ግን በተለይ መንግሥታት ከሃይማኖታዊ ጥገኝነት የተላቀቁበት ዘመን ነበር ማለት ይቻላል፡፡ በዚህ ዘመን መጀመሪያ ላይ ተስፋ ፈንጥቆ የነበረው መሃይምነትን የመቅረፍ ‹የመሠረተ ትምህርት› ዘመቻም፣ በዘመኑ መጨረሻ ላይ ጠውልጎ ነበር፤ ሕዝቦች ለፖለቲካዊ ተሳትፎ የነበራቸው ጉጉት በፍራቻ መቀመቅ የወረደውም በዚህ ዘመን ነው፣ - የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ስልጣኔ
የማርክሲስትን የስልጣኔ ዘመን (በአገራችን) ተክቶ የመጣው የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ስልጣኔ አጀማመሩ ላይ ለካፒታሊዝም የቀረበ ቅይጥ ኢኮኖሚ መር ስልጣኔ ለመሆን ቢሞክርም፣ የኋላ ኋላ ሶሻሊስታዊ ዴሞክራቲክ ኢኮኖሚ መር የሚመስል የስልጣኔ ዘመን ሆኗል፡፡ ዘመኑን በይፋ ‘የሕዳሴ ዘመን’ ብሎ ለመጥራት በመንግሥት የታወጀ ሲሆን፣ በተለይ ለአንደኛ ደረጃ (አውራ) መንገዶች እና ሕንጻ ግንባታ ትኩረት የሰጠ የስልጣኔ ዘመን ነው፡፡ በዚህ ዘመንም፣ ልክ እንደ ማርክሲስታዊው የስልጣኔ ዘመናችንም ሁሉ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊው የስልጣኔ ዘመን ለሰብኣዊ ልማት ምንም ትኩረት ያልሰጠ፣ ትምህርት ከጥራት ይልቅ በቁጥር የተመዘነበት እና በአስተዳደሩ ርዕዮተ ዓለም አስፈጻሚነት የተከረከመ ትውልድ ከማፍራት በላይ ያልተጋ ዘመን ነው ለማለት የሚያስደፍር ትውልድ ተፈጥሯል፡፡
አሁን ያለንበትን ዘመን ስንታዘበው፥ አንድም አያቶቻችን ባኖሩልን የኩሩነት፣ የጨዋነት እና የሥነ ምግባር መመሪያ ሳንታነፅ አሊያም ሉላዊነት (globalization) ዘልቆን ከሰለጠኑት ዓለማት እኩል በሐሳብ ሳንራመድ – እንዲሁ የባከንን ትውልድ ሆነን መቅረታችን ያሳስበኛል፡፡ የዚህ ብክነት መፍትሔው – መማር እና ማንበብ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ነገር ግን እንደ ትውልድ የትምህርት ዕድሉንም ሆነ እውነተኛ ለውጥ አጎናፃፊ ትምህርት ወይም የሚለውጥ ንባብም ሆነ ማንበቢያ በማጣት እየተሰቃየን እንደሆነ ሳስብ ደግሞ ስለራሳችን አዝናለሁ፡፡
ዳያስፖራው ጽንፈኛ ወይስ ተስፈኛ?
- በተለምዶም የአስተያየቱን ጽንፉን ተመልክቶ ‹የዲያስፖራ ፖለቲካ›› የሚባል ስያሜ እየተሰጠው ይገኛል፡፡ የ‹የዳያስፖራ ፖለቲካ› ውስጥ በብዛት ጽንፉ ወዲህ ወይም ወዲያ ይሆን ይሆናል እንጂ ፅንፍ መያዙ አይቀርም የሚለው እምነት የብዙዎች እየሆነ ነው፤ እንዲያውም አንዳንዶቹ ሁለቱንም ጽንፎች አዳርሰዋል በሚል ሰለሞን ተካልኝ በማስረጃነት ያነሳሉ፡፡
- ዳያስፖራው እኛ (በአገር ውስጥ ነዋሪዎች) የማናውቀውን የዴሞክራሲ ጣዕም የሚያውቅ፣ እኛ የሌለን የፖለቲካ ምኅዳር ያለው፣ ገሚሱ ኑሮው ሞልቶለት የወገኑ ጉዳይ ከሩቅ የሚቆረቁረው የለውጥ ተስፈኛ እንጂ ጽንፈኛ ሊባል አይገባውም የሚሉት ደግሞ በሌላ ወገን ይገኛሉ፡፡
- በገዢው ፓርቲ በአሸባሪነት የተፈረጀው እና ግዝፈቱ እና አስፈሪነቱ በቴሌቪዥን የሚደሰኮርለት ግንቦት ሰባት እስከአሁን ድረስ የሠራው ሥራም ሆነ ያሸበረው ሽብር ምን እንደሆነ ቢጠየቅ፣ ተቃውሟቸውን በይፋ ለሚገልፁ ሰዎች ‹‹ባጅ›› በመሆን ለመንግስት ከማገልገል ውጪ ይሄ ነው የሚል መልስ ለማግኘት አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሽግግር ምክር ቤት መነሻዬ ያለውን ለኢትዮጵያ የስርዓት ለውጥ የተዘጋጀ የሽግግር መንግስት የማዋቀር ሥራውን ትቶ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የሞት ቀን ላይ (እንደ መረጃ ሰጪ ሚዲያ) የጦፈ ክርክር በማድረግ የትኩረት አቅጣጫውን ስቶ ታይቷል፡፡ ሲመሠረት በሁለት ወራት ውስጥ፣ የአቶ መለስ ኅልፈት ከተሰማ ወዲህ ደግሞ በሁለት ሳምንት ውስጥ የኢትዮጵያን ሕዝብ ነጻ አወጣለሁ ብሎ ቃል የገባው ይሄው የሽግግር መንግስት ቃሉ ከተግባሩ የፈጠነ መሆኑ ሌሎች የዳያስፖራ ቡድኖችንም ሆነ እራሱን ከተኣማኒነት ዝርዝር ውስጥ በዚህ መንገድ እንዳያወጣ ያሰጋል፡፡
- EAC (Ethiopian Americans Council) በመባል የሚታወቀው ቡድን በተቃራኒው፣ በተቃራኒው ለኦባማ ደብዳቤ ከመጻፍ አንስቶ፣ በልማት ሰበብ የሚገኙ የእርዳታ ገንዘቦች ነጻነትን ማፈኛ እንዳይወሉ የማንቂያ ደውል ለአሜሪካ መንግስት በመደወል እየሰሩ ያሉት የሚበረታታ ነው፡፡ የጋራ ንቅናቄ የተባለውም ቡድን በተለይ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የአቋም መግለጫ ጽሑፎችን በማውጣት ይታወቃል፤ አሁንም እንኳን በቅርቡ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ለውጥን የሚጠይቅ ግልጽ ደብዳቤ አሰራጭቷል፡፡ የHR2003 (የሰብኣዊ መብት ጉዳይን ያስቀደመ መመሪያ) የአሜሪካ መንግስት የኢትዮጵያ መንግስት ላይ እንዲጥል አሊያም እርዳታ እንዲያግድ የሚያደርገውን ዶሴ በማርቀቅ እና እንዲፀድቅ እና አገር ውስጥ ለውጥ እንዲመጣ ጫፍ ደርሶ የነበረ ትግል የታገሉትም የዳያስፖራ ቡድኖች ናቸው፡፡ ይህንን በምክንያት ከመሟገት እና ለውጥን ከመወትወት ወይም የ‹‹አራማጅነት›› ሚና የተሻለ የሚሠሩ እና ሊበረታቱ የሚገባቸው አሉ፡፡
- የተቃውሞ ሰልፎች እና ስብሰባዎች ላይ የሚሳተፉ እነዚህ ለፖለቲካው ጤንኝነት ደንታ የማይሰጣቸው ሰዎች ‹‹ጥገኝነት›› ፈላጊዎች ግንባር ቀደም እና አርማ ተሸካሚ ሆነው በፎቶ እና ቪዲዮ ማኅበራዊ አውታሮች ላይ በአጋጣሚ የሚመለከቱ እና ግለሰቦቹን የሚያውቋቸው የአገር ቤት ሰዎች ጠቅላላ የዳያስፖራውን እንቅስቃሴ በግለሰቦቹ ዓይን የመዳኘት እና በኢቴቪ ፕሮፓጋንዳ ‹‹ጥገኝነት ለመጠየቅ ሲሉ›› የሚለውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ስለሚሆን፣
- ግለሰቦቹ የጥገኝነት ወረቀታቸውን ካገኙ በኋላ ተመልሰው ትግሉን ስለማይቀጥሉበት፣ መጣ ቅርት የሚሉ አራማጆችን መመልከቱ/መከታተሉ ተስፋ ስለሚያስቆርጥ፣
- ግለሰቦቹ ወረቀቱን እስከሚያገኙ ድረስ ፖለቲካዊ ተሳትፏቸውን ለማጉላት እና ተቃዋሚነታቸውን ለማሳመን ጽንፍ ድረስ ስለሚጓዙ የጠቅላላውን ዳያስፖራ መልክ በአንድ ላይ የማጉደፍ ኃይል አላቸው፡፡
በተለይ በጉዳዩ ላይ ከዚህ በፊት በተነሱ አስተያየቶች ዳያስፖራው ለሚታማበት ጽንፈኝነት የራሳቸውን ምክንያት የሚዘረዝሩ አሉ፡፡ ከነዚህ ምክንያቶች ውስጥ እኛ (በአገር ውስጥ ነዋሪዎች) በባሕላዊ አስተሳሰቦች እና በዴሞክራሲ መብት እጦት የታፈነ ማኅበረሰብ ውስጥ የነጻነትን ትክክለኛ ትርጉም እና ጣዕም በአግባቡ ማጣጣም ባለመቻላችን የመጣ ክፍተት እንደሆነ የሚናገሩ አሉ፡፡ በተጨማሪም፣ አንዳንዴ የነጻነትን ትክክለኛ ጣዕም ያጣጣሙ ስደተኞች ያን ዓይነቱ ለውጥ ወደአገር ቤት በተቻለ ፍጥነት እንዲመጣ ማሰባቸውም ለአንዳንድ ስህተቶች እንደሚዳርጋቸው ይታመናል፡፡ ዞሮ፣ ዞሮ እዚህም ያለነው ወይም እዚያ ያሉት የምንታገለው ለጋራ ለውጥ ስለሆነ እነርሱም እኛን፣ እኛም እነርሱን የምናደምጥበት መድረክ እና ቋንቋ ያስፈልገናል፡፡
የኢሕአዴግ ስርዓት፤ ፍጹም የበላይነት ወይስ የሕግ የበላይነት?
አፋዊነት… (Sweet Talk)
በተግባር መስካሪ አንድም እንዳይጠፋ” ይህ የእዮብ መኮንን ዘፈን ግጥም የዚህን ጽሑፍ ገዢ ሐሳብ ይገልፃል፡፡ ሲነገር ከንፈር የማያደናቅፍ፣ ሲደመጥ ጆሮ የማይኮረኩር፣ በአዕምሮ ሲሰላሰል የማይጎረብጥ በተግባር መሬት ላይ የማይተገብሩት የአፍ ፈሊጥ /leap service/ በከተማችን በርክቷል፡፡ በጊዜ ብዙ ሰዎችን ታዝበናል፡፡ “ድሮም ትልቅ ነበርክ” የሚል የግጥም ፉካሬ በጌትነት እንየው ከመስማት በላይ፣ በፍትህ ጋዜጣ “መንግስት መዶሻ ነው፤ ሕዝብ ደግሞ ምስማር” ሲለን ከነበረ አምደኛ “ግድቡ በአቶ መለስ ይሰይም”፣ “ምስላቸው በብር ይታተም” የሚል ጭብጥ የያዘን ተውኔት ድርሰት ከማየት በላይ፤ ወደ መልካምም ወደ ክፉም አገራችንን በሚመራው በዛች ቀውጢ ሰዐት ፍፁም ከሚያምኑት “Meles Zenawi is back in town” የሚል ዘገባ ከማንበብ በላይ፤ “አገር ማለት የኔ ልጅ” የሚል ውብና ጥልቅ መልዕክት ያለው ግጥም ገጣሚ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ በፍትህ ጋዜጣ አምደኛ በሆኑ ማግስት ለጠ/ሚሩ መታሰብያ ግጥም መድረክ ላይ ሲያነበንቡ ከማየት በላይ ሌላ የመከዳት ስሜት የሚፈጥር ምን ነገር አለ?! ምንም የለም! ይህ ጽሑፍ የአቶ መለስ ዜናዊን መልካም ያልሆነ አስተዳደር ለመተችት የተነሳ አይደለም፡፡ ወትሮም አቶ መለስ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ የሚበጀንን ነው የሚያደርጉት ብለው ሲሞግቱ ለነበሩትም አይደለም፡፡ ክፉ ናቸው፤ በደለኛ ናቸው የሚል ወንጀል ሲያቀርቡ የነበሩት ሲሞቱ ደግሞ በተቃራኒው መላዕክትነታቸውን ሲሰብኩ ለከረሙት ታዝበናል፣ አይተናል ለማለት ነው፡፡ የቀድሞ ጠ/ሚ ተፈጥሯዊ ሞት የአንዳንድ ግለሰቦች ጭንብል አስወለቀ እንጂ ይህ ችግር በአደባባይ መታየት ከጀመረ ሰንበቷል፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ ራሳቸው የተሳተፉበት “እንደገና” የተሰኝ ዘጋቢ ፊልም ላይ እንዲህም የሚል የአፍ ፈሊጦችን አድምጠን ነበረ፡፡
“
ዋናው ሕሊና ነው… ሕሊና ደግሞ ከሁሉም በላይ ነው መሆን ያለበት! ፍትሕ፣ ስርዓት ሁል ጊዜ ፐርፌክት አካሄድ ከሄደ በዚች ምድር፣ በዚች አገር ምንም አይከሰትም፡፡”(አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ) ይህን የተናገረው በ1997 ምርጫ ምክንያት በታሰሩ የፓለቲካ እስረኞች እና መንግስት መሐል በሽምግልና የተሰየመው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ ነው፡፡ ወዳጄ እንደሚለው ኃይሌ እግረ ብርሃን እንጂ ልበ ብርሃን እንዳልሆነ አልዘነጋሁም፡፡ ሆኖም ግን በአፈጠጠ እውነት ላይ ተደራድሮ እስረኞቹን የ12 ዓመት ሕፃን ባንክ እንዲዘርፍ ልከን አሳስተን ነው ያስገደልነው የሚል የይቅርታ ሰነድ ሕሊናው እየተመለከተ ፈርመዋል፡፡ ያን ጊዜ ሕሊናውን ከወዴት ሰውሮት እንደነበረ አላውቅም፡፡ በየትኛው የሞራል እርከን ላይ ቆሞ ሰለሕሊና እንደሚሰብክም አይገባኝም፡፡ ዛሬ የስፖርት ጋዜጠኛ ፍስሐ ተገኝና የመሳሰሉት ሕሊና እያለን ያልተፈፀመውን የ11 ዓመት ታዳጊ ባንክ ሊዘርፍ ነበር የሚል ዜና አላነብም ሲሉ ከአገር ተሰደው እየኖሩ ነው፤ እነኃይሌ በአንፃሩ ዋናው ነገር ሕሊና ነው እያሉን ነው፡፡ ታዲይ ይህ ምንድን ነው… ይህ የአፍ ፈሊጥ ነው፡፡
“ዋናው ነገር አባይን እገድባለሁ ብሎ ማሰቡ ነው ትልቅ የሚያደርገን … ለእኔ አባይን እንገድባለን ብለን ‘ማሰባች’ ነው ዋናው ቁም ነገሩ!…አገራዊ ጉዳዮችን መለየት አለብን፤ ያለንበት 21ኛው መቶ ክፈለ ዘመን የተለያዩ ፓርቲዎች፤ የተለያዩ ርዕዮት ዓለሞች፣ የተለያዩ የአሠራር መንገዶች የተለያዩ ነገሮች ያለበት ነው፡፡ እብርነት ውበትነት የሆነበት ዘመን ላይ ነው ያለነው፤ ከዚህ ውጭ መሆንም አንችልም፡፡ ግን እንደገና ደግሞ እነዚህን ሁሉ የሚያስተባብር አንድ ነገረ አለ፤ እርሱም ኢትዮጵያ የሚባል ነገር አለ …የፖለቲካ ፓርቲዎች ልንመሠርት የምንችለው፣ ልንከራከር የምንችለው፣ አሸንፈን ፓርላማ ልንገባ የምንችለው፣ ተሸነፈን ልንወርድ የምንችለው፣ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ስትኖር ነው፡፡”
(ዳንኤል ክብረት)
ጤናማ ሞራል እንዲኖረን በጽሑፉ የሚተጋው፣ታሪኩን የዘነጋ ትውልድ እንደተፈጠረ በበሰለ ጽሑፍ ሸንቆጥ የሚያደርገው፣ ወጋችንን ተረታችንን መዘንጋት እንደሌለብን የሚያስታውሰው፣ ከድንጋዩ ይልቅ ሰዉ ክቡር እንደሆነ የሚመክረው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በቀረበው ዘጋቢ ፊልም ከተናገረው የተቀነጨበ ነው፡፡ ከአፄ ልብነድንግል ጀምሮ አባይን ለመገደብ ሐሳብ የነበራቸውን ነገሥታት ታሪክ ዋጋ በማሳጣት ዛሬ እንገድባለን ብለን ‘ማሰባችን’ ብቻ “ትልቅ” እንደሚያደረገን ሰብኮናል፡፡ ኢትዮጵያ የምትባል ነገር ያለ ሕዝብ ነጻነት በፍትሕ ላይ ባልተመሰረተ የፖለቲካ አስተዳደር ልትፀና እንደምትችል ከታሪክ አስታዋሻችን ምክር እየተለገሰን ነው፡፡ ይህ የዳንኤል ንግግር ከአፍ ፈሊጥነት እና ገዢው ፓርቲ ላዘጋጀው ፕሮፓጋንዳ ማጣፈጫነት የዘለለ ምን ውሃ የሚያነሳ ነገር አለው? …ምንም! ይሄም የአፍ ፈሊጥ ነው!
እነዚህ ለአስረጅነት ቀረቡ እንጂ በፖለቲከኛው፣ በኪነ ጥበበኛው፣ በጋዜጠኛው፣ በነጋዴው፣ በሐኪሙ እና በሌሎችም በቀላሉ ማንም ሊያስተውለው የሚችል አገራችንን ወግቶ የያዘ ችግር ነው፡፡ ይህ አፋዊነት በዚሁ ከቀጠለ በአገራዊ ደረጃ የሚያመጣው ልክ ያልሆነ የትውልድ አስተሳሳብ ብዙ ዋጋ ያስከፍላል፡፡
ከ“አሲምባ ተራራ” ላይ ውረዱ!
“የአያቶቻችን ቤት፥ ይሁን ባዶ፣ ይሁን ኦና
በኛ ቁመት፣ በኛ መጠን አልተቀለሰምና፡፡” (ግጥሙን በቃሌ ስለወጣሁት ቃላት ልገድፍ እችላለሁ!) ከአሁን በፊት የነበረው ትውልድ “አሲምባ ተራራ” ላይ ያስወጣው ድንጋይና ሳሩ አይመስለኝም፡፡ ወጣት ግምባር ላይ ጥይት የሚያሰድድ፣ የሴት ልጅን ጡት የሚያስቆርጥ፣ ከአንድ ማሕፀን የወጡ ሁለት ወንድማማቾችን ጎራ አስለይቶ የሚያታኩስ አስተሳሰባቸው ነው ወደ አሲምባ ተራራ ላይ ያስወጣቸው፡፡ ‹ያ ትውልድ› ዘመኑ ያፈራውን አስተሳሰብ አላምጦ ለአገሬ የሚበጃት ይህኛው ሕሳቤ ነው የሚል ስሌት ላይ ጽኑ እምነት ጨምሮ ውድ የሆነውን ሕይወቱን ያለምንም ፍርሐት ከፍሏል፡፡ ከፋም ለማም ‹ያ ትውልድ› ይበጃል ያለውን አድርጓል፡፡ አሁን የ‹ያ ትውልድ› ክሽፈት ታሪክ መዝገብ ወይም ትውልዱ አብሰልስሎ አገሪቱ ያስመለሳትን ሐሳብ የምንወቅጥበት ጊዜ ላይ አይደለንም፡፡ ኢሕአፓ፣መኢሶን፣ ሰደድን እያጣቀሱ፤ ፋኖ ተሰማራን እየፎከሩ ሕዝቡ ከተጨበጠበት የፍርሐት ቆፈን ለማላቀቅ መሞከር ዘመንን ያለማገናዘብ በጥልቅ ያለማሰብ ችግር ነው፡፡ ገዢው ፓርቲን የሚሞግት የሚያሳጣ ፓሊሲ፣ ተቋም፣ መዋቅር እና የፖለቲካ ርዕዮት ዓለሙ ላይ ከመመራመር ይልቅ እገሌ ደርግ ነበር፣ ኢሕአዴግ ጣኦት ነው፣ ሰውዬው ኤርትራዊ ነው፣ አራማጅ ነኝ፣ ሕዝብ ፈሪ ነው፣ መብራት ተቆረጠ፣ መብራት ተቀጠለ ሐሳቦች እኛን አያነቁም፡፡ ሕዝቡ ከተከናነበው የፍርሐት ጃኖም አያላቅቅም፡፡ ዛሬ እንደ በፊቱ ኧረ ጎራውን ብቻ ፎክሮ፣ ቀረርቶ አቅራርቶ፣ እንደው በደፈናው በሽላላ የምትነቃ ኢትዮጵያ አይደለም ያለችው፡፡ ይህን መሳይ ችግር በብዛት በጋዜጣ ጸሐፊዎቻችን የሚስተዋል ነው፡፡ ይሄን ዘመን ያገናዘበ የዚህን ትውልድ ጥያቄ መመለስ የሚችል አስተሳሰብ ያነገበ አገርን ወደፊት ሊያራምድ የሚችል ጽሑፍ ብናገኝ ነው የራሳችንን አሲምባ መፍጠር የምንችለው፡፡ እንደው በደፈናው ኢሕአዴግ ክፉ ነውና ደረታችሁን አቀብሉ ሐሳብ አሁን ያለውን አምባገነናዊ ስርዓት ያጸና እንደሆነ እንጂ ለአገር አይበጅም፡፡ በ1997 ዓ.ም. ባልተመረመረ ፖለቲካ ደረታችንን አቀብለን የከፈልነው ዋጋ የሚዘነጋም አይደለም፡፡ መድኀኒቱን ስጡን
“ቃልን መርጠን ከየቤቱ
ለመናገር መጎምዥቱ
ለእኛስ ነው ወይ መዳኃኒቱ?” ችግራችንን በተለያዩ ተረቶችና ምሳሌዎች መዘርዘር የአዋቂነት ልኬት የመሆን አዝማሚያ ይስተዋላል፡፡ ፔዳል፣ ብስክሌት፣መዶሻ፣ ምስማር፣ድስትና ክዳን፣ የግሪክ አፈ ታሪኮች፣ የአበው ተረቶችን እያጣቀሱ በሽታችንን ማብራራት አሳቢነት (Thinker) አይደለም፡፡ ሲታከክልን ዝም ብለን እንጂ ቁስሉን አዝለን ከምንዞረው ከኛ በላይ በሽታውን የሚያውቅ የለም፡፡ አሁን ያለው ስርዓት ለአገራችን ፈፅሞ እንደማይበጃ ከኑሮ በላይ የሚያስረዳ ነገር የለም፡፡ ደራሲዎች፣ ገጣሚዎች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ጸሐፊዎች በመንደር ከሚወራው በተሻለ ለአደባባይ የሚበቃ ሐሳብ አለኝ እና ወደ ጋዜጣ መጥቻለሁ ስትሉ የበሽታውን መድኀኒት ጠቁሙን፤ አብዮታዊ ዲሞክራሲ የሚለው መርሕ አይበጀንም ስትሉ የሚበጀንን ርዕዮተ ዓለም አሳዩን፡፡ ይሄ መንግስት መውረድ አለበት ስትሉ፣ እንዴት መውረድ እንዳለበት መንገዱን ስጡን፡፡ በደፈናው ስለተበደልን ብቻ ሕይወታችሁን ማግዱ አትበሉን፡፡ እንደው ብድግ ብሎ ሕዝብ ቄጤማ ነው የሚል ፈሊጥ አንስቶ የቄጤማን ልፍስፍሰነት እየተነተኑ ሕዝቡ ፈሪ እንደሆነ መተንተን ተራማጅነት አይደለም፡፡ ይሄ ፈፅሞ ለአገርም አይረዳም፡፡ ማቅ ልበስ፤ ውደቅ በንስሐ
“እንደ ቶን ፍም እሳት ይፋጃል ይልሳል
መንገዱ ከሲኦል ያደርሳል፤
የደበቅከው እውነት ሳይጮህ በበረሃ
ማቅ ልበስ ውደቅ በንስሐ”
(አቤል ሙሉጌታ)
ዛሬ ይርጋለም ዱባለንና ሰለሞን ተካለኝን እየኮነኑ በደላቸውን ሊያጥቡ እየሞከሩ ነው፤ ዛሬ የራሳቸውን ጉድፍ ሳይነቅሉ ሌላው ንስሐ እንዲገባ እየሞገቱ ነው፡፡ በሁለት በኩል ተስላችሁ፣ እምነት አጉድላችሁ፣ ለስጋችሁ አድልታችሁ፣ ንዋይ አሳውሯችሁ፣ ዝና ባርቆባችሁ፣ እውቀት ስንክሎባችሁ፣ ሌላም ሌላም ምክንያት ኖሯችሁ በደል ስለፈፀማችሁ ወግዱ ሂዱ ለማለት ተፈልጎ አይደለም፡፡ የአፍ ፈሊጣችሁ በእምነት ከሆነ እንሞግታችሀለን፤ በስህትት ከሆነም ይቅር እንላችኋለን፡፡ ሁለት አሥርት ዓመታት በስቃይ ለመሩን መሪ ለአንድ ቀንም ቢሆን ከልብ አዝነናል፤ ለይቅርታ ፍፁም ቅርብ መሆናችንን ያመላክታል፡፡ እኔ ስለአቶ መለስ ዜናዊ አንባቢነት ነው የጻፍኩት፣ የኔ ተቋም ይቅርታ ጠይቋል፣ የሰው እንጂ የራሴን ግጥም አላነበብኩም ዓይነት ሰንካላ ሰበብ ክደቱን አያክምም፡፡ ሁሉም ለፈፀመው በደል የራሱ የሆነ ምክንያት አለው፡፡ በቀጣይነት አምነናችሁ ብርሃናችሁን እንድንቀበል፣ ያለጥርጣሬ ፍሬያችሁን እንድናጣጥም አጥጋቢ የሆነ ማብራሪያ አሊያም ከልብ የሆነ ይቅርታ ይገባናል፡፡ ይሄ በደላችሁን ያጥባል፤ “ነጥቆ እንዳልነጠቀ ማባበል” ሕሊናችሁን አይበጀውም፡፡
ከአፍ ፈሊጥ በዘለለ ጥረት አድርጋ በነበረችው ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ በአሜሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ባደረገችው ንግግር ሐሳቤን እቋጫለሁ፡፡
“…የዚህ ፕሮግራም ዋና ዓላማ እንደሚመስለኝ ኢትዮጵያን ማወደስ ነው፡፡ እያሰብኩት ነበረ… እውን ኢትዮጵያ የምትወደስ ናት ወይ እያልኩኝ… ይሄን በሐቀኝነት ስንመልስ ብዙ ቅር የሚያሰኙ ነገሮች አሉ፡፡ ከቅሬታም በላይ የሆኑ፤ ምክንያቱም ኢትዮጵያ የነጻነት አገር አይደለችም፡፡ ኢትዮጵያ የፍትሕ አገር አይደለችም፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬም ዜጎቿ በድህነት የሚኖሩባት በሐፈረት የሚያቀረቅሩባት፣ ብዙ ዜጎቸ የሚሰደዱባት ነች፡፡ ስለዚህ እናወድሳት ውይ ብለን እንጠይቅ፡፡… አይ መወደስማ አለባት የሚል አቅም ነው ያለኝ፡፡ ስናወድሳት ግን ምን አስበን ነው? ኢትዮጵያ ታላቅ አገር ነበረች፤ ይህን እኔ አይደለሁም የምናገረው ታሪክ ነው የሚመሰክረው መልዕክቴ ይሄው ነው:: ኢትዮጵያ ልትወደስ የሚገባት ታላቅ አገር ነች! ታለቅነትን ለማየት ግን ሁሌም በአንድነት እንቁም… አንድነታችን ሁላችንንም የሚያቅፍ… ሁላችንንም የሚያሰባስብና የኢትዮጵያ የጋራ መኖሪያነት በሚያውቁት ይሁን፡፡”
(ብርቱካን ሚደቅሳ)
አሜን ይሁን! … “አንድነታችን ሁላችንንም የሚያቅፍ፤ሁላችንንም የሚያሰባስብና የኢትዮጵያ የጋራ መኖሪያነት በሚያውቁት ይሁን”… ይሁን!
መፅሃፍ፤ ከወዴት አለህ?
የዓለም ሃይማኖቶች እና ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት
ይህን ስናደርግ በእኔ እምነት “የክርስቲያን ደሴት” ወይም “ኢስላማዊት በሸሪአ የምትመራ ኢትየጵያን” ከመስበክ ይልቅ የጋራ ቅኝቶችን የሚደግፉና ለአዳዲስ አስተሳሰቦች በር የሚከፍቱ ቤተ እምነቶች ይኖሩናል፡፡ ነገር ግን እኛን የሚወክል ሀገራዊ ሁኔታዎችን ያገናዘበ ስርዓትን ተባብረን በሰላማዊ መንገድ ካልጠየቅን ምን አልባት በፈጣሪ ለማመን ፍቃድ መጠየቅ ሊኖርብንም ይችላል፡፡ በፈጣሪ መኖር አላምንም ብንል ደግሞ በፓርቲችን ማመን ግዴታህ ነው የሚባልበት ዘመን ሩቅ አይሆንም፡፡ጽሑፌን ሁሉን በሚያስማማው እና ‹‹በአንተ ላይ ሊደረግ የማትፈልገውን በሌላው አታደርግ›› በሚለው ድንቅ ዓረፍተ ነገር ስዘጋ ልቤን ደስ እያለው ነው፡፡
የታክሲ ሰልፍ መጀመሪያውና መጨረሻው
አሁን ሰልፉም ቢሆን መጀመሪያውና መጨረሻው (ጫፍ ለጫፍ) መተያየት የማይችልበት ደረጃ እየደረሰ ስለሆነ ጠዋት ሥራ ለመግባት ያሰበ ሰው ተራው እስኪደርሰው ሲጠብቅ አይውልም፡፡ ስለዚህ የሚመለከተው ክፍል /መንገዶች እና ትራንስፖርት ባለስልጣን/ ዘላቂ እርምጃ ዛሬውኑ /ሳይቃጠል በቅጠል/ መተግበር ካልጀመረ ወደማይወጣበት አዘቅት እኛንም ራሱንም መውሰዱ ነው፡፡
አንድ ለመንገድ፡- ከካምፖሎጆው ፍጥጫ ማግስት
ጸሐፊውን ለማግኘት በኢሜይል አድራሻቸው tamrattesfaye39@yahoo.comይጻፉላቸው፡፡
የኛ ኃይል
ከሚዲያው የሚመነጭ ጤናማ የአደባባይ ተዋስኦ በጠፋበት በፕሬሱ የጨለማ ዘመን ማግስት አዲስ ነገርን ማግኘት ለጤናማ ሕዝባዊ ውይይቶች መከፈት አስተዋጽዖ የነበረው ከመሆኑም በላይ ጋዜጣዋ መንግስትን በጠንካራ መልኩ በመተቸት ብትታማም የገዥውን ፓርቲ አቋም የሚያንጸባርቁ ቋሚ አምደኞች ነበሯት፡፡ አሁን በሥራ ላይ የሚገኙ እና ታዋቂ የሆኑ የሚዲያ ተቋማትም ቢሆኑ ራሳቸውን ሲገልጹ አዲስ ነገርን ማነጻጸሪያ ሲያደርጓት ተስተውሏል፡፡
በኢትዮጵያ የፕሬስ /ሐሳብን በነጻ የመግለጽ/ ነጻነት እያሽቆለቆለ ለመምጣቱ የአዲስ ነገር ጋዜጠኞችን እንኳን የሚያሠራ ክበብ አለመፈጠሩ ዐብይ ምስክር ነው፡፡ ዛሬ በዓለም የጡመራ ተግባር ቀን ጋዜጣዋን እና ጋዜጠኞቹን ማስታወስ ያስፈለገንም ለዚሁ ነው፡፡ ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት፣ የሕዝብ ድምጽ /የሕዝብን ብሶት/ የሚያስተጋባ፣ የሕዝብን መንፈስ የሚያነቃቃ ጋዜጣ ያስፈልገናል፡፡ አዲስ ነገር ጋዜጣ የፈጠረችው እና ለመግደል የሚያስቸግር መንፈስ ቢኖር ይኸው መንፈስ ነው፡፡ ዓመታት አልፈውም “ዛሬም በአዲስ ነገር የማይደራደር ትውልድ” ለመፍጠር በቅታለችና!!!