Monthly Archives: July 2012
ፎንቱ ፎኒፍ ሪፈታ ጄናን ኢቲሌን ጂቢቻ ቲ ካቴ ("ስጋ ለስጋ ይደነግጣል ቢባል ጥጃ እንኳ በቁርበት ደነገጠች")
ፖካ ዮኬ፣ IDIOT PROOF; ETHIOPIA
ጋዜጣና መጽሔቶቻችን ከሰኞ እስከ ሰኞ – ስምንት
- እኛ የምንታገለው ለሥርዓት ለውጥ እንጂ ለመንግስት ለውጥ አይደለም – አቶ ጥላሁን እንደሻው ለፍኖተ ነፃነት
- መድረክ ወደግንባር መሸጋገሩን አበሰረ፤ አዲስ የአመራር አባላት መርጧል (ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር (መድረክ) ይባላል፡፡) – ፍኖተ ነፃነት
- የሙስሊሙ ጉዳይ ኢሕአዴግን ከፋፈለ፤ ግንባሩ ለድክመቱ ራሱን ወቅሷል – ሰንደቅ
- የኮንዶሚኒየም ቁጥሮች፤ 207ሺኅ 069 ቤቶች (እስካሁን የተገነቡት)፣ 119ሺኅ 431 ቤቶች (ለተጠቃሚዎች የተላለፉ)፣ 87ሺኅ 638 (የት እንደገቡ ያልተገለፁ) – ሰንደቅ
- ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውጭ አገር እረፍት ላይ ናቸው፣… Weekly Fetehe remains in limbo፣…. የካሉብ የነዳጅ ልማት ስምምነት ተሰረዘ፣…. የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንትና ምክትላቸው ከኃላፊነት ተነሱ፣… ሐበሻ ሲሚንቶና ሐበሻ ቢራ ከአክሲዮን ድርሻቸው ለአፍሪካና ለአውሮፓ ኩባንያዎች አካፈሉ፣… ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ፍትሕ ጋዜጣን አላትምም አለ – ሪፖርተር (ረቡዕ፣ ቅዳሜ እና እሁድ)
- ፍትህ ጋዜጣ እንደታገደ ነው፤ አዘጋጆቹ ከማተሚያ ቤት ፍትሕ ሚኒስቴር ሲመላለሱ ዋሉ – አዲስ አድማስ
- የላሊበላ ነዋሪዎች ሊነሱ ነው – አዲስ አድማስ
‹‹በአሥራ አንዱ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስትያናት ዙሪያ ለበርካታ ዓመታት ሲኖሩ የቆዩ ነዋሪዎች፤ ለቅርሱ ደህንነትና ለገፅታው ማማር ሲባል ሊነሱ እንደሆነ የጠቆሙት ምንጮች፣ ነዋሪዎቹን በተመረጡ ሦስት ቦታዎች ለማስፈር የ፹፼ ሚሊዮን ብር በጀት እንደተያዘ ታወቋል…›› - WHO TO WATCH? Ethiopia’s olymic medals bid – Fortune
ኢትዮጵያውያን በለንደን ኦሎምፒክ ለሜዳልያ የሚሻሙባቸው ውድድሮች ከመጪው አርብ ጀምሮ ቅዳሜ፣ እሁድ፣ ሰኞ፣ ማክሰኞ፣ ረቡዕ እና እሁድ ዕለት እንደሚካሄዱ ጋዜጣው አትቷል፡፡
- ከመንግስት መረጃ የማግኘት መብት አለን – ፍኖተ ነፃነት
- የኮንዶሚኒየም አፈፃፀም ሳንካዎች በ40/60 የቤት ልማት ዕቅድ አንዳይደገም ጥንቃቄ ቢደረግ – ሰንደቅ
- ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ – ሪፖርተር (ረቡዕ)
- ‹‹የመጣነው መንገድ›› ብቻ ሳይሆን ‹‹የምንሄደው መንገድም›› ያሳዝናል እንዳንል – አዲስ አድማስ
- አንድ ሰው ስንት ነው? – አዲስ ጉዳይ
- ያበረ ድር ሁሉ አንበሳን ያስራል ማለት አይደለም – ሪፖርተር (እሁድ)
‹‹…ነገር ግን ድር ካበረ ሲባል ባዶ መግለጫና የፌስቡክ ጨዋታ አይደለም፡፡ አስመራ ውስጥ ያበረ ድር ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አንበሳ ያስራል ማለት አይደለም፡፡ የውስጥ ጥንካሬና አንድነት የሌለው ድር እንኳን አንበሳን ሊያስር ሲወጥሩትና ሲጠመዝዙት የሚቆራረጥና የሚበጣጠስ ይሆናል፡፡ ድሩ ጠንካራ ካልሆነ፣ የድሩ ጥንካሬ በሚገባ ካልተፈተሸና ካልተረጋገጠ ድር ስለተባለ ብቻ ያስራል ማለት አይደለም፡፡ በቀላሉ ይበጣጠሳል ማለት ነው፡፡…››
ባልቻን ፍለጋ
<<ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ፣መድፍ አገላባጭ፣ ብቻ ለብቻ፡፡>>
ደከመኝ ሰለቸኝ፣ እረፍት የማያውቀው፣አብዮታዊ መሪ፣ ጓድ መንግስቱ ነው፡፡
ከሌሎች ሀገሮች ህገ መንግስቶች በተለየ የኢፌድሪ ህገ-መንግስት ገበየሁ ቢሞት የባልቻ መገኛ የት እንደሆነ በግልፅ አይጠቁምም፡፡ ይልቅስ ህገ መንግስቱ ገበየሁ ‹በማይኖር ጊዜ› በሚል ጥቅል አጠራር ምክትሉ ‘የባልቻን’ ድርሻ ይወርሳል ይላል፡፡ ይህ ህገመንግስታዊ አንቀፅ ለትርጉም ክፍት ነው፡፡ ‘ገበየሁ’ ከስራ ለአጭር ጊዜ ሲርቅ ነው ብቻ ነው ተብሎ ሊተረጎምም ይችላል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አይ ‘ገበየሁ’ በሞተም ጊዜ ተክቶ ሊሰራ ይችላል ተብሎ ሊተረጎም ይችላል፡፡ እንግዲህ ‘ባልቻን’ ከህጋዊ መስመር አገኘን የሚሉም ከሁለተኛው ትርጉም የተነሳ መሆን አለባቸው፡፡ አሁን ካለው ድባብ በመነሳት ይህ የመሆን ዕድሉ ዝቅተኛ ይመስላል፡፡ ቢሆን እንኳን እንደ ‘ገበየሁ’ ህዝቡን ብቻውን ማገላበጡ ያጠራጥራል፡፡
እነሆ ‘ባልቻን’ ፍለጋ የጦር ካምፕ ውስጥ ነን ‘ባልቻን’ በግልፅ ለማየት ግን አልተቻለም፡፡ በርግጥም ‘ባልቻን’ ከጦር ካምፕ የምናገኝው ከሆነ ግን ጉዳዩ ያስፈራል፡፡ ቢያስፈራም ግን ‘ባልቻ’ በጦር ካምፕ ውስጥ መሽጎ ሊሆን ይችላል፡፡ የተገኝ እለት ‘ጀኔራል ባልቻ’ ሀገሪቱን በአንድ እግሯ አቆሟት መባሉ የማይቀር ነው፡፡
በርግጥም ‘ባልቻን’ ከምድረበዳ ያልነው ‘ከተቃዋሚው’ ጎራ ይመጣ ይሆን የሚለውን ግምታችን ነው፡፡ ዲያስፖራ ተቃዋሚው መግለጫ፣ ኮምኒኬ ወ.ዘ.ተ በማውጣት ዱብ ዱብ እያለ እራሱን እያሟሟቀ ይገኛል፡፡ መቸም ‘ባልቻ’ ‘አትላንቲክን’ ወይም ‘ሚድትራኒያንን’ አለዚያም ‘መረብ’ ወንዝን አቋርጦ ሊመጣ ይችላል ማለት ከባድ ነው! ኧረ በጣም ከባድ ነው፡፡ በሌላ ጎኑ ሀገር ውስጥ ያለውን ተቃዋሚ ስናይ አሁን ባለበት ሁኔታ ጀኔራሎቹ፣ ይሆኑ ወይስ ከቤተ መንግስት እያለ ከመገመት ውጭ ያው በምድረበዳ እየተንከራተተ ነው፡፡ እናም አንድ ነገር ላይ እርግጠኛ መሆን እንችላለን አዎ ‘ባልቻን’ በምድረ በዳ መፈለግ ከንቱ ልፋት ነው፡፡
ባርነት በዘመን ሲዋጅ?
ይህ የነጻነትን ጣእም በቅጡ ያለመረዳት ችግር የሚቀረፍበትን መንገድ በቀላሉ አግኝተን የምንለውጠውም አይመስልም፡፡የነጻነትን ጣእም ያለመረዳት ችግር ባይሆንም ኖሮ ለዘመናት የባርነትን እና ገዢዎችን እያፈራረቅን አንኖርም ነበር፡፡ ይህ አዙሪት መቼ ይሆን የሚያበቃው?
ማን ስልጣን ላይ ተወለደና?
- አስፈራርቶ እና በጠብ-መንጃ ተማምኖ ከሚገዛን ልምድ ያለው አምባገነን አንድ ሀገራዊ ራዕይ ፈጥሮ የሚመራን ጀማሪ ይሻለናል፣
- ተቃዋሚዎችንና ጋዜጠኞችን ሳስር እና ሳንገላታ አያገባችሁም፣ ገንዘባችሁን በሊማሊሞ በኩል ይዛችሁ መሄድ ትችላላችሁ፤ ሃያ አንድ ዓመት ማሸነፍ ያቃተን የምግብ እህል ተረጂዎች ጉዳይ ግን የጋራችን ነው ብሎ ሀገሪቷን ከሚያዋርድ መሪ በግልፅ ቋሚ የውጭ እገዛ የምንፈልግበትን ሀገራዊ ጉዳይ ለይቶ ከሁሉም ወዳጅ ሀገራት ጋር ተስማምቶ የሚሰራ መሪ ይሻለናል፣
- ስልጣን ላይ ለመቆየት ንፁሀን ዜጎችን ከሚገድል/ከሚያስገድል ይህን ተግባር እፈፅማለሁ፣ ሀገሪቷን ከእህል ተረጂነት አላቅቃለሁ አለበለዚያ ግን ስልጣን የናንተ ነውና እለቃለሁ የሚል፣ ብሎም የሚፈፅም መሪ ይሻለናል፡፡
ምናልባት፣ ምናልባት… ከመለስ በኋላስ?
ከቅርብ ሰዎች ተገኙ የተባሉት መረጃዎችም የሚያሳዩት ገና ካሁኑ ለሁለት የተከፈሉ እና ለቦታው ራሳቸውን ያጩ ጎራዎች መኖራቸውን ብቻ ነው፡፡ የተባለው መረጃ እውነት ሆኖ የትኛውም ውስጠ ፓርቲ ቡድን ቢያሸንፍ እንኳን አዲሱ እጩ ወደ ስልጣን የሚመጣበትን መንገድ የፓርቲዎቹ ሕግጋቶች የሚመልሱት ጥያቄ አይመስልም፡፡ የፓርቲ መሪዎቹን የቆይታ ጊዜ የማይገድብ የፓርቲ ሕገ ደንብ እንዲህ ዓይነቱን ሁኔታ የሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት ምን ዓይነት ስልቶች እንደሚመጡ መገመት አስቸጋሪ ነው፡፡ ጉዳዩ በተለያየ አተያይ የተወሳሰበ ቢመስልም የትኛውንም ነገር ያስከፍል እንጂ የኅወሓትን የፓርቲ የበላይነት አረጋግጦ የሚጠናቀቅ እንደሚሆን የብዙዎች ግምት ነው፡፡ በእርግጥ ይህ አዲስ መሪ የማምጣት ትግል የውስጠ ፓርቲ መረጋጋት ላይም የራሱን ተጽዕኖ መፍጠሩ የማይቀር ነው፡፡ አቶ መለስ ለዓመታት የገነቡትን እምነት እና በየሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ቢሮ መግለጫ ላይ ሳይቀር የሚከሰት ስብእና ማጣት፣ የአባላትን በራስ መተማመን መጉዳቱ የማይቀር ነው፡፡ በተለይ በተለይ እንደኢሕአዲግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አባላት ባሉበት ፓርቲ ውስጥ የመረጋጋቱ ሁኔታ ጊዜ የሚወስድ ይሆናል፡፡ ይህ የውስጠ ፓርቲ መረጋጋት እና መለስን የሚተካ አዲስ ምሰሶ የማቆም ሥራ ከፓርቲው ውጪ ለሆኑ የፓለቲካ እንቅስቃሴዎች አዲስ ዕድል ይከፍት ይሆናል የሚሉ ግምቶችንም ፈጥሯል፡፡
ይህ የአመራር ክፍተት አሉ እየተባሉ የሚጠሩትን አገር ውስጥ ከሚገኙት ፓርቲዎች ውጪ ያሉ የተለያዩ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችም ቢሆን፣ አሁን ባላቸው በግልፅ የማይታይ እና የማይነገር የፖለቲካ እንቅስቃሴ ላይ ተመርኩዞ ወደ ላይ ብቅ ይላሉ ብሎ ማሰብ ዘበት ነው፡፡ (ክፍተቱ ለተለያዩ እንቅስቃሴዎች የተወሰነ ዕድል መስጠቱ የማይቀር ቢሆንም!)
በዚህ መሀል፣ እንደሕዝብ – የአቶ መለስን የውጪ ተክለ ስብዕና የሚተካ ጠንካራ ሰው ማምጣት የሚጠበቅበት አዲሱ አመራር በዕድሉ ተጠቅሞ የፓርቲውን የዲሞክራሲ ባህል መለወጥ ካልቻለ የአቶ መለስን ዓይነት ሌላ ሰው፣ በዘዴ ሁሉን የመጠቅለል ክህሎት እስኪያዳብር ድረስ ‹‹የአንባገነንት መለማለጃ ልንሆን ይሆን እንዴ?›› የሚል ጥያቄ ከወዲሁ ማንሳቱ አስፈላጊ ነው፡፡
መለስ ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያውያን
ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ Diciphering Meles Zenawi’s haterade to Ethiopia በሚለው አንድ በቅርቡ ባሳተሙት ጽሑፋቸው ‹ኢትዮጵያን ሳይወዱ ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ ብቸኛ መሪ› በሚል በአቶ መለስ ላይ የሚሰነዘሩ ትችቶችን ባጠናከሩበት ጽሑፋቸው አቶ መለስ ሀገራቸውን የማይወዱበትን ምክንያት የተለያዩ የስነልቦና ኀልዮቶች በማንሳት አስረድተዋል:: በብሔር ብሔረሰቦች መብት መረጋገጥ ስም በርካታ የብሔር ሥራ ፈጣሪዎች (Ethnic entrepreneurs) በየሰፈሩ እንዲፈለፈሉ ምክንያት ሆነዋል የሚል ትችትም ከአቶ መለስ ስም ጋር በተደጋጋሚ የሚነሳ ጉዳይ ነው:: አቶ መለስ አንደበተ ርቱዕ እንደሆኑ በደጋፊዎቻቸው ቢመሰከርላቸውም ሌሎች ግን ‹በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነበሩ የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮችን በማንጓጠጥ እና አግባብ ያልሆኑ ቃላትን በመጠቀም ይናገራሉ፤ ይህም ከአንደበተ ርቱዕነት አቅም ማጣት የሚመነጭ ነው› በማለት በተቃራኒው ይተቿቸዋል:: የኢትዮጵያ ታሪክ ለነገሥታቱ የሚወግን ታሪክ በመባል በሚዛናዊነት በተለያዩ ወገኖች ይወቀሳል፡፡ ቀጣዩ የኢትዮጵያ ታሪክስ፣ ከመቶ ዓመታት በኋላ የአቶ መለስን ታሪክ እንዴት ያስታውሰው ይሆን?
ጋዜጣና መጽሔቶቻችን ከሰኞ እስከ ሰኞ – ሰባት
- ኢትዮጵያን አይዶል ክብሩን ያጣ ፕሮግራም ነው፣ ባለሙያዎቹ ምንም ነገር የማያውቁ ናቸው ተብያለሁ – አቶ ይስሐቅ ጌቱ (የኛ ፕሬስ)
- የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መራራ የዕድገት ሽሙጦች፤ 140 ሺ ቶን ጫት በየዓመቱ ይቃማል፣ 7 ቢሊዮን ብር ለጫት ፍጆታ ይውላል – መሰናዘሪያ
- አንድነት በሰላማዊ ትግል ለሚመጣ ችግር ኃላፊነቱን እወስዳለሁ አለ፤ ለጠ/ሚስትሩ መልካም ጤንነት ተመኝቷል፡፡ – አዲስ አድማስ
- ከኮሌስትሮል ነፃ የሚባለው የፓልም ዘይት ነፍሰገዳይ መሆኑን ያውቃሉ? – ኢትዮ ቻናል
- ንግድ ባንክ የሚድሮክ የሚድሮክ ኩባንያዎችን በ942 ሚሊዮን ብር ብድር አንበሸበሸ – ሪፖርተር (እሁድ)
- ስርዓቱ በጥቅም ላይ መገንባቱ ውሻ በቀደደው ጅቦች እንዲገቡ አድርጓል – መሰናዘሪያ
- ታጋዩን በማሰር ትግሉን ማሰር አይቻልም! – ፍኖተ ነፃነት
- የሕዝበ ሙስሊሙ ጥያቄዎች አሁንም ግልጽ ምላሽ ይሻሉ – ሰንደቅ
- የብብታችንን ሳንጥል የቆጡን ለማውረድ እንሞክር – ሪፖርተር (ረቡዕ)
- እየነገርናቸው ሲያዩት እንደዋዛ
ከተለበለበው የተላጠው በዛ – የወሎ ሰው (አዲስ አድማስ) - ታሪካዊ ግዳጅ በአክራሪነት ላይ – ኢትዮ ቻናል
- ተዓማኒነቱ በሚያጠራጥር ስታትስቲክስ ከመፎከር እውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር – ሪፖርተር (እሁድ)